Polly po-cket
free book gift

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።


Iqra

=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=

ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ


1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።

2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።

3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።

4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።
Iqra
Iqra

Homeየወጣቱ ተልዕኮ ምንነትየአቂዳ ትምህርቶችየሶላት መመሪያረመዷንሙስሊም ሴቶችኢስላማዊ ቤተሰብከታሪክ ማህደርሐዲስለወጣቶችትምህርትና መሰረታዊ ክህሎታችጤናችንግጥምጥያቄና መልስኢስላማዊ መዝገበ ቃላት
free book gift

=<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=

ያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም አንብብ!

free book gift

በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።

free book gift

አሏህ በቂያችን ነው


ጉዳዮችን ለአሏህ በመተው ፤ በሱ መማካት ፤ ቃሉን ማመን ፤ ፍርዱን መቀበል ፤ በሱ መተማመን እና የችግሮቻችንን መፍትሔ ከሱ መጠበቅ እጅግ ከላቁ የኢማን ፍሬዎች ውስጥ ይጠቀሳሉ። ታላላቅ ከሆኑ የሙእሚኖች ባህሪም ውስጥ ይቆጠራል። አንድ የአሏህ ባሪያም የጉዳዮቹ ፍፃሜ ያማረ መሆኑን አውቆ ሲረጋጋና በሁሉም ጉዳዮቹ በጌታው ሲመካ እንክብካቤን ፣ ቀረቤታን ፣ ድጋፍንና ድልን ያገኛል። ኢብራሂም(ዐ.ሰ) እሳት ውስጥ ሲወረወሩ «ሐስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል» አሉ። በዚህም አሏህ እሳቷን ቀዝቃዛና ሰላም አደረገላቸው። መልእክተኛችንም(ሰ.ዐ.ወ) እና ባልደረቦቻቸው በከሃዲዎችና በጣኦት አምላኪ ጦረኞች ሲከበቡ «ሐስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል» አሉ።

--<({አል-ቁርአን 3:174})>--

«ከአሏህም በሆነ ፀጋና ችሮታ ክፉ ነገር ያልነካቸው ሆነው ተመለሱ ፤ የአሏህን ውዴታ ተከተሉ አሏህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው።»

የሰው ልጅ ብቻውን ክስተቶችን ታግሎ ማሸነፍና ችግሮችን መቇቇም አይችልም። ምክኒያቱም ደካማና መላ-ቢስ ተደርጎ ተፈጥሯልና። ሆም በጌታው ሲመካና ጉዳዮቹን በሙሉ ወደሱ ሲያስጠጋ ከሚሸሸው ነገር ሊድን ይችላል። አለበለዚያ መከራዎች ሲፈራረቁበት እና ችግሮች ሲያካብቡት የዚህ ድሃና ደካማ ባሪያ መላው ምን ሊሆን ይችላል?

--<({አል-ቁርአን 5:23})>--

«ምእመናንም እንደኾናቸው በአሏህ ላይ ተመኩ አሉ»

በመሆኑም ነፍህን መገሰፅ የምትፈልግ ሆይ! ኃያል ብርቱና የፀጋ ባለቤት በሆነው አሏህ ተመካ፤ ከጭንቀት እንዲያላቅህና ከችግሮች እንዲያድንህ የዘወትር መፈክርህና ድስኩርህ «ሐስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል» ይሁን። ገንዘብህ ቢቀንስ ፣ ብድር ቢጠራቀምብህ ፣ የገቢ ምንጮችህ ቢደርቁ «ሐስቡነሏህ ወኒእመል ወኪል» ብለህ ተጣራ፤ በሽታ ቢይዝህ ስቃይ ቢበረታብህ ችግሮች ቢደራረቡብህ «ሐስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል» በል። የጠላትህን ሴራ ከፈራህ ወይም በደለኛን ከሰጋህ ወይም ድንገተኛ ክስተት ካስደነገጠህ «ሐስቡነሏህ ወኒዕመል ወኪል» በል።

--<({አል-ቁርአን 25:31})>--

«መሪም ረዳትም በጌታህ በቃ»


512

የወጣቱ ተልዕኮ አድራሻ
free book gift

Download Islamic Books
ኢስላማዊ መጽሐፎችን ያውርዱ

Important Web Links


free book gift

free book gift

free book gift

ስለወጣቱ ተልዕኮ ምንነት ለማወቅ እዚህ ላይ ክሊክ ያድርጉ

Copyright©Youth-Mission የወጣቱ ተልዕኮ